የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ተጨማሪ 3 ሰዎች ተገኙ

By Tibebu Kebede

March 31, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥርም 25 መድረሱን የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ይህ መረጃ እስከ ተዘጋጀበት ሰዓት ድረስ በአጠቃላይ 1013 የላቦራቶሪ ምርመራ ያደረገ ሲሆን ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 66 የላብራቶሪ ምርመራ አካሄዶ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ተጨማሪ ሶስት (3) ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጧል፡፡