አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ብሔራዊ የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ከተዋቀረ በኋላ ባሉት አምስት ቀናት ውስጥ ብቻ ከሀገር ውስጥ 150 ሚሊየን ብር መገኘቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ገለፁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ በፌስቡክ ገፃቸው ባስተላለፉት መልእክት “ብሔራዊ የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ከተዋቀረ በኋላ ባሉት አምስት ቀናት ውስጥ ብቻ የኢትዮጵያን ሕዝብ ደግነት ለመመልከት ችለናል” ብለዋል።