የጸረ-ሙስና ቀን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ በአዳማ ከተማ እየተከበረ ነው
አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 10፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጸረ-ሙስና ቀን በኦሮሚያ ክልል ደረጃ ለ17ኛ ጊዜ በአዳማ ከተማ እየተከበረ ነው፡፡
በስነ-ስርዓቱ ላይ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ – ጉባኤ ሰዓዳ አብዱረሀማንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት ስራ ሃላፊዎች እና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡
ቀኑ ሙስናን መታገል በተግባር በሚል መሪ ቃል ነው እየተከበረ የሚገኘው፡፡