የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 26 ደረሰ

By Tibebu Kebede

March 31, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ተጨማሪ አንድ ሰው በኮሮና ቫይረስ መያዙን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

በአጠቃላይ በኮሮናቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥርም 26 መድረሱን የጤና ሚኒስቴር ማምሻውን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።