የሀገር ውስጥ ዜና

በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 29 ደረሰ

By Tibebu Kebede

April 01, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 23፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ተጨማሪ ሶስት ሰዎች ባለፉት 24 ሠዓታት መገኘታቸውን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ አስታወቁ።

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 68 የላቦራቶሪ ምርመራ አካሂዶ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ተጨማሪ ሶስት ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጧል፡፡