የሀገር ውስጥ ዜና

የፌዴራል ፍ/ቤቶች ለተጨማሪ 23 የስራ ቀናት በከፊል ዝግ ሆነው እንዲቆዩ ተወሰነ

By Tibebu Kebede

April 01, 2020

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 23 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ከአርብ መጋቢት 25 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለተጨማሪ 23 የስራ ቀናት በከፊል ዝግ ሆነው እንዲቆዩ ተወሰነ፡፡

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንት ወይዘሮ መአዛ በሰጡት መግለጫ በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ስርጭት አመላካቾች አስጊ መሆናቸውን ጉዳዩ የሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት በመግለጽ ላይ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።