አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 23 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ከአርብ መጋቢት 25 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ለተጨማሪ 23 የስራ ቀናት በከፊል ዝግ ሆነው እንዲቆዩ ተወሰነ፡፡
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንት ወይዘሮ መአዛ በሰጡት መግለጫ በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ስርጭት አመላካቾች አስጊ መሆናቸውን ጉዳዩ የሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት በመግለጽ ላይ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።