አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 23 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በ200 ሚሊየን ዶላር በአዳማ ኢንዱስትሪያል ፓርክ እየተገናባ የሚገኘው የአልባሳት ክር ማምረቻ ፋብሪካ የመጀመሪያው ዙር ግንባታ ተጠናቀቀ።
ኪንግደም የክር ማምረቻ ኩባንያ በአዳማ ኢንዱስትሪያል ፓርክ በሁለት ዙር በአፍሪካ ትልቁን የክር ፋብሪካ እየገነባ እንደሚገኝ የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አበበ አበባየሁ በትዊተር ገፃቸው ላይ አስፍረዋል።