Fana: At a Speed of Life!

ለጋምቤላ ክልል የ36 ዘመናዊ ትራክተሮችና 150 የውሃ መሳቢያ ጀነሬተሮች ድጋፍ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ለጋምቤላ ክልል 36 ዘመናዊ ትራክተሮችና 150 የውሃ መሳቢያ ጀነሬተሮች ድጋፍ አድርጓል፡፡

የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አይሻ መሀመድ÷ ክልሉ ሰፊ መሬትና ውሃ የታደለ እንደመሆኑ የግብርና ሜካናይዜሽን ግብዓቶቹ መሬቱን ከውሃ ጋር በማገናኘት አደጋ የመቋቋም አቅምን ለማሳደግ ብሎም ምርታማነትን ለማምጣት ትልቅ እገዛ ያደርጋል ብለዋል፡፡

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኡሞድ ኡጁሉ በበኩላቸው ÷ ለተደረገው ድጋፍ አመስግነው ድጋፉ ክልሉ በግብርና ዘርፍ የጀመረውን ተግባር የሚያግዝና ከአርሶ አደሩና አርብቶ አደሩ እየቀረበ ያለውን የሜካናይዜሽን ግብዓት አቅርቦት ጥያቄ የሚመልስ ነው ማለታውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.