የሀገር ውስጥ ዜና

ጠቅላይ አቃቤ ህግ ለተጨማሪ 1 ሺህ 559 ታራሚዎች ይቅርታ መደረጉን ገለፀ

By Tibebu Kebede

April 02, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ለተጨማሪ ለ1 ሺህ 559 ታራሚዎች ይቅርታ መደረጉን በዛሬው እለት አስታውቋል።

የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በጉዳዩ ላይ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፥ ይቅርታ የተደረገላቸው ታራሚዎቹ በየፖሊስ ጣቢያ የነበሩ፣ በማረሚያ ቤት ውስጥ መረጃቸው በወቅቱ ለውሳኔ በሚመች ሁኔታ ተጣርቶ ያልቀረበ እንዲሁም የፌደራል ታራሚዎች ሆነው በየክልሉ የነበሩ ታራሚዎች ናቸው።