Fana: At a Speed of Life!

የተለያዩ ሀገራት አዲስ ዓመታቸውን እየተቀበሉ ነው

አዲስ አበባ ፣ ታኅሣሥ 22 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎርጎሮሳውያን የዘመን አቆጣጠር ቀመር የሚጠቀሙ ሀገራት አዲሱን ዓመት 2023 እየተቀበሉ ነው፡፡

በዚህ መሰረትም በመካከለኛው ፓስፊክ ባሕር የምትገኘው ኪሪቲማቲ ደሴት አዲሱን ዓመት 2023 ከተቀበሉ የመጀመሪያ ሀገራት ውስጥ አንዷ ናት፡፡

በተጨማሪም ኒውዝላንድ እና አውስትራለያ የጎርጎሮሳውያኑን 2023 አዲስ ዓመት በደመቀ የርችት ሥነ-ሥርዓት በመቀበል ቀዳሚ ሀገራት መሆናቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.