ዓለምአቀፋዊ ዜና

የተለያዩ ሀገራት አዲስ ዓመታቸውን እየተቀበሉ ነው

By Alemayehu Geremew

December 31, 2022

አዲስ አበባ ፣ ታኅሣሥ 22 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጎርጎሮሳውያን የዘመን አቆጣጠር ቀመር የሚጠቀሙ ሀገራት አዲሱን ዓመት 2023 እየተቀበሉ ነው፡፡

በዚህ መሰረትም በመካከለኛው ፓስፊክ ባሕር የምትገኘው ኪሪቲማቲ ደሴት አዲሱን ዓመት 2023 ከተቀበሉ የመጀመሪያ ሀገራት ውስጥ አንዷ ናት፡፡

በተጨማሪም ኒውዝላንድ እና አውስትራለያ የጎርጎሮሳውያኑን 2023 አዲስ ዓመት በደመቀ የርችት ሥነ-ሥርዓት በመቀበል ቀዳሚ ሀገራት መሆናቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡