የሀገር ውስጥ ዜና

ሀዋሳና ጎንደርን ጨምሮ ከተሞች የኮሮናቫይረስን ለመከላከል የተለያዩ ክልከላዎችንና ውሳኔዎችን እያሳለፉ ነው

By Tibebu Kebede

April 02, 2020

አዲስ አበባ፣መጋቢት 24፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ሀዋሳ እና ጎንደርን ጨምሮ ሎሌች ከተሞች የኮሮናቫይረስ (ኮቪድ-19) ስርጭትን ለመከላከል የተለያዩ ክልከላዎችንና ውሳኔዎችን እያሳለፉ ነው።

በሀዋሳ ከተማ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ስርጭት ለመከላከል ተጨማሪ ክልከላዎች መጣላቸውን የከተማዋ ምክትል ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ገልፀዋል።