የሀገር ውስጥ ዜና

ታላቁ የህዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያውያን የአስተሳሰብም ሆነ የተግባር ከፍታ ነው- ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ

By Tibebu Kebede

April 02, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ታላቁ የህዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያውያን የአስተሳሰብም ሆነ የተግባር ከፍታ ነው ሲሉ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ገለፁ።

የኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ሣህለወርቅ ዘውዴ የህዳሴ ግድቡን ግንባታ 9ኛ ዓመት በማስመልከት ባስተላለፉት መልዕክት፦ “ዛሬ መጋቢት 24 የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የተጀመረበትን ዘጠነኛ ዓመት እያሰብን ነው” ብለዋል።