የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ ከቱሉ ሞዬ ጂኦተርማል ጋር 800 ሚሊየን ዶላር የሚያወጣ የኃይል ግዢ ስምምነት ተፈራረመች

By Tibebu Kebede

April 02, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2012  (ኤፍ.ቢ.ሲ) ኢትዮጵያ ከቱሉ ሞዬ ጂኦተርማል ጋር 800 ሚሊየን ዶላር የሚያወጣ የኃይል ግዢ ስምምነት በዛሬው እለት ተፈራረመች።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ እንዳስታወቁት፥ በዚህ ደረጃ በመንግሥትና በግል መካከል አጋርነት ሲመሠረት በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።