Fana: At a Speed of Life!

የፓን አፍሪካኒዝም ሻምፒዮን የተማሪዎች  የእግር ኳስ ውድድር  ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 2ኛው የፓን አፍሪካኒዝም ሻምፒዮን የተማሪዎች  የእግር ኳስ ውድድር   በአዳማ ከተማ ተጀምሯል፡፡

በማስጀመሪያ መርሃግብሩ  የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ዋና ፀሃፊ ባህሩ ጥላሁን ÷ የፓን አፍሪካኒዝም ሻምፒዮን   ውድድር ተተኪ ስፖርተኞችን ከማፍራት አንፃር ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ጠቁመዋል፡፡

የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዲኤታ አምባሳደር መስፍን ቸርነት በበኩላቸው÷መሰል ውድድሮች  ተተኪ ስፖርትኞችን ከማፍራት ባሻገር ክልሎች እርስ በእርሳቸው ግንኙነታቸውን የሚያጠናክሩበት መድረክ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

በውድድሩ ስድስት የወንድና አራት የሴት የእግር ኳስ ቡድኖች  ተሳታፊ ሲሆኑ÷ ውድድሩን በድል የሚያጠናቅቁ ቡድኖች ለ2ኛ ጊዜ በታንዛኒያ በሚካሄደው የፓን አፍሪካ ሻምፒዮን ተሳታፊ  እንደሚሆኑ  ከባህልና ስፖርት ሚኒስቴር  ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ውድድሩ ለተከታታይ ሶስት ቀናት እንደሚቆይም ተገልጿል፡፡

በሰላማዊት ተስፋየ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.