Fana: At a Speed of Life!

በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ በተከሰተ የእሣት አደጋ ንብረት ላይ ጉዳት ደረሰ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛሬው ዕለት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ ገነት ሼዶች ተብሎ በሚጠራው ቦታ በተከሰተ ድንገተኛ የእሣት አደጋ በንብረት ላይ ጉዳት ደረሰ፡፡

ከቀኑ 9:40 የተከሰተው ይህ የእሣት አደጋ በስድስት ሼዶች ላይ ጉዳት ማድረሱን ከክፍለ ከተማው ከሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

የእሳት አደጋው ተጨማሪ ጉዳት ሳያደርስ በቁጥጥር ሥር የዋለ ሲሆን ÷የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.