ስፓርት

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ ሞሮኮ የሚያደርገውን ጉዞ ጀምሯል

By Mikias Ayele

January 04, 2023

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለቻን ውድድር ዝግጅት ወደ ሞሮኮ የሚያደርገውን ጉዞ ጀምሯል፡፡

ብሔራዊ ቡድኑ ዛሬ ወደ ግብፅ ካይሮ በረራ ያደረገ ሲሆን ፥ ቡድኑ ከደቂቃዎች በፊት በሰላም ካይሮ መድረሱ ታውቋል፡፡

ብሔራዊ ቡድኑ ለትንሽ ደቂቃዎች በካይሮ አየር ማረፍያ ቆይታ ካደረገ በኋላም ወደ ሞሮኮ ጉዞውን የሚቀጥል መሆኑን ከእግር ኳስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡