Fana: At a Speed of Life!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሆራ ኢንዱስትሪን ጎበኙ

አዲስ አበባ ፣ ታኅሣሥ 26 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በገላን ከተማ የሆራ ኢንዱስትሪን ጎብኝተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ዛሬ በገላን ከተማ የ’’ኢትዮጵያ ታምርት’’ ሁለተኛው ጉብኝት በሆራ ኢንዱስትሪ ማድረጋቸውን አስፍረዋል፡፡

በዚህ ኢንዱስትሪ ዘመናዊ የቡና ማቀነባበሪያ ፣ መቁያ እና ሲሚንቶ ማሸጊያ ማምረቻ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ነው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የገለፁት።

ኢንዱስትሪ ማሳዳግ ለሀገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ማስገኛ ትልቅ ሚና እንዳለውም አስፍረዋል ::

በድጋሚ በ’’ኢትዮጵያ ታምርት’’ ተሳታፊ እንሁን ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.