ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ አጋሩ
አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ አጋርተዋል ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአዲስ አበባ ከተለያዩ ክፍለ ከተሞች ከተውጣጡ አረጋውያን ፣ አካል ጉዳተኞች እና የጎዳና ተዳዳሪዎች ጋር የገናን በዓል አሳልፈዋል።
በመርሐ ግብሩ 150 ሰዎች ተገኝተዋል።
በአልዓዛር ታደለ