Fana: At a Speed of Life!

ቻይና በኮቪድ-19 ሳቢያ ያሳለፈችውን የውጭ ሀገር የጉዞ ገደብ አነሳች

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ቻይና በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ያሳለፈችውን የውጭ ሀገራት የጉዞ ገደብ አነሳች፡፡

ከአሁን በኋላ ወደ ቻይና የሚገቡ የውጭ ሀገር ተጓዦች ቀደም ሲል በተቀመጠው የኮቪድ -19 አስገዳጅ መመሪያ መሠረት በለይቶ ማቆያ ለአምሥት ቀናት እንደማይቀመጡ አልጀዚራ ዘግቧል፡፡

ቢጂንግ ገደቡን ካነሳች ወዲህ የመጀመሪያዎቹን 387 መንገደኞች ከሲንጋፖር እና ከካናዳዋ ቶሮንቶ ከተማ መቀበሏ ተመላክቷል፡፡

መንገደኞቹም ቀደም ሲል በሀገሪቷ በተጣለው የኮቪድ -19 ገደብ መሠረት ሳይንገላቱ ከወዳጅ ዘመዶቻቸው ጋር መቀላቀላቸው ነው የተገለጸው፡፡

ቀደም ሲል ቻይና እየተባባሰ በሄደው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሥርጭት ምክንያት ድንበሮቿን ላለፉት ሦስት ዓመታት ዘግታ መቆየቷ ይታወሳል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.