የሀገር ውስጥ ዜና

በቀይ መስቀል ማኅበር ለትግራይ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት 15 ተሽከርካሪ ተበረከተ

By ዮሐንስ ደርበው

January 08, 2023

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር አሥር አምቡላንሶችና አምስት ቀላል ተሽከርካሪዎችን ለማኅበሩ ትግራይ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት አስረከበ፡፡

ድጋፉ የተገኘው ከዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ፕሬዚዳንት አበራ ቶላ የሰብዓዊነት እሳቤን በሕብረተሰቡ ውስጥ ለማፅናት መሥራት ይገባል ብለዋል፡፡

በማኅበሩ የትግራይ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ  ብርሃኑ መኮንን÷  ድጋፉ ሰብዓዊ አገልግሎቱን ለማስቀጠል ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳለው ገልጸዋል፡፡

ጽሕፈት ቤቱ ወደነበረበት ተመልሶ ሰብዓዊ አገልግሎቱን በክልሉ በስፋት እንዲያደርስ አጋር አካላት ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!