Fana: At a Speed of Life!

የማሌ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “ዶኦማ” እየተከበረ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የማሌ ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ በዓል “ዶኦማ” በሌሞ ጌንቶ በተለያዩ ዝግጅቶች እየተከበረ ነው፡፡

የማሌ ብሔረሰብ በደቡብ ኦሞ ዞን ከሚገኙት 16 ብሔር ብሔረሰቦች አንዱ ሲሆን÷ በየዓመቱ ጥር 1 ወይም በብሔረሰቡ አጠራር “ባሬ ፔተ” አዲሱን ዓመት ይቀበላሉ።

“ዶኦማ”÷ ማብሰር፣ መጀመር፣ መቅመስ፣ መክፈት፣ ቅድሚያ የሚሉ ፍቺዎች እንዳሉት ከጋሞ ዞን ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

በአከባበር ሥነ ስርዓቱ ላይ÷ የፌደራል፣ የክልል፣ የአጎራባች ዞኖችና ወረዳዎች፣ የጋሞ ዞን አመራሮች፣ የጋሞ አባቶች እንዲሁም ከሰሜን ኬንያ፣ ጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ቦርጂ፣ ኮንሶ፣ ባስኬቶ እና ሌሎች አካባቢዎች የመጡ እንግዶች በሌሞ ጌንቶ ተገኝተዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.