የሀገር ውስጥ ዜና

ጥቅም ላይ እንዳይውሉ የተከለከሉ የእጅ ንጽህና መጠበቂያዎች

By Feven Bishaw

April 03, 2020

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 25 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ሳይመዘገቡና የብቃት ማረጋገጫ ፍቃድ ሳያገኙ የተለያዩ ግለሰቦችና ተቋማት በህገ ወጥ መልኩ የእጅ ንጽህና መጠበቂያ (Hand sanitizers) ነው በማለት አምርተው ገበያ ላይ እያቀረቡ በመሆናቸው ህብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ጠየቀ።

ባለስልጣኑ በአዋጅ በተሰጠው ስልጣንና ኃላፊነት የምግብና መድኃኒት አስመጪዎች፣ አከፋፋዮችና አምራች ድርጅቶች የብቃት ማረጋገጫ ፍቃድ እንደሚሰጥ ይታወቃል።