ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ ከፈረንሳይና ጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የአውሮፓ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ካትሪን ኮሎንና እና ከጀርመን የፌደራል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አናሌና ባየርቦክ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንዳሰፈሩት ፥ ጥልቅ እና ፍሬያማ ውይይታችን ኢትዮጵያ ከፈረንሳይ እና ከጀርመን ጋር ያላትን ጠንካራ እና የቆየ ግንኙነትን የሚያንፀባርቅ ነው ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፥ ኢትዮጵያ ባለፉት አራት ዓመታት እያከናወነች ያለችውን ዘርፈ ብዙ ማሻሻያ፣ ቁልፍ ውጤቶችንና ተያያዥ ችግሮችን አካፍለዋል።
ኢትዮጵያ ከፈረንሳይ እና ከጀርመን ጋር ያላት ግንኙነት ለበርካታ ዐሠርት ዓመታት መቆየቱንም ነው ያነሱት።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለው ፥ ባለፉት አራት ዓመታት ከሁለቱም ሀገራት ለተደረገው ያልተቋረጠ ድጋፍ አመስግነዋል።
ሁለቱ ሚኒስትሮችም ለውጡን ለማስቀጠል የሚያደርጉትን እገዛ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ማረጋገጣቸውን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!