አዲስ አበባ፣ መጋቢት 26፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የመጋቢት 27 የዐቢይጾም 7ኛ ሳምንት የሰንበተ ክርስቲያን ቅዳሴ ከጠዋቱ 11:30 ጀምሮ በአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ አዲስ ቴሌቪዥን በቀጥታ እንደሚተላለፍ ተገለፀ።
ዕለቱ ዓመታዊ የመድኅኔዓለም በዓል በመሆኑ ለመላው ሕዝበ ክርስቲያን እንኳን አደረሳችሁ ያለዐው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በመንበረ ፓትርያርክ የተስፋ ልዑክ ዐቢይ ግብረ ኃይል በዕለቱ የማይቆርቡ ምእመናን ቅዳሴውን በቤታቸው በሱባኤ ባሉበት ሁነው እንዲሰሙ፣ በጸሎት እንዲተጉ በማሰብ የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔን ለማስተፈጸም የተደረገ መሆኑን አስታውቋል።