Fana: At a Speed of Life!

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በለሚ ኩራ በ90 ቀናት እየተሠሩ ያሉ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ጥር 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በለሚ ኩራ በ90 ቀናት እየተሠሩ ያሉ ፕሮጀክቶችን ጎበኙ፡፡

ከንቲባዋ በለሚ ኩራ በ90 ቀናት እየተከናወኑ የሚገኙ የመንገድ አካፋይ የአረንጓዴ ልማት፣የአቅመ ደካሞች የጋራ መኖሪያ ቤት ግንባታ፣ የእንጀራ ማምረቻ ማዕከል፣የወተት ከብት እርባታ ፣ኮንቬንሽን ማዕከል እንዲሁም አዲሱን የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ህንፃንና የመንገድ የመሠረተ ልማት ስራ ያለበትን ደረጃ ነው የጎበኙት።

በጉብኝታቸውም ፥ በክፍለ ከተማው በግንባታ ላይ ያሉ ፕሮጀክቶች በተወሰነላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ ለማድረግ እየተደረጉ ያሉ ጥረቶችን አድነቀዋል፡፡

በቀሪ ስራዎች ላይም በተሻለ ትጋትና ቁርጠኝነት በመስራት በጋራ የምናስበው ስኬት ላይ መድረስ እንደሚቻል በጉብኝቱ ወቅት ገልጸዋል።

በክፍለ ከተማው እየተገነቡ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶች በበጎ ፍቃደኛ ሀገር ወዳድ በሆኑ ኢትዮጵያውያን ባለሀብቶች እንደሆነ መገለጹን ከከንቲባ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.