ስፓርት

በሙምባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ

By ዮሐንስ ደርበው

January 15, 2023

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ ማለዳ በሕንድ በተካሄደው የሙምባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች አሸነፉ።

በሴቶች ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1ኛ እስከ 8ኛ ተከታትለው በመግባት በበላይት አጠናቀዋል፡፡

በውድድሩ አትሌት አንቺዓለም ሃይማኖት 2 ሰዓት ከ24 ደቂቃ ከ15 ሰከንድ በመግባት የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻል ጭምር አሸንፋለች፡፡

አትሌት ረሂማ ቱሳ እና አትሌት ለተብርሃን ኃይላይ 2ኛ እና 3ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል፡፡

በወንዶች አትሌት ለሚ ብርሃኑ 2 ሰዓት ከ7 ደቂቃ ከ32 ሰከንድ በመግባት የቦታውን ክብረ ወሰን በማሻሻል አሸንፏል፡፡

ኬንያዊው አትሌት ፊልሞን ሮኖ 2ኛ ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ኃይሉ ዘውዱ 3ኛ ደረጃን ይዘው ውድድሩን ጨርሰዋል፡፡