Fana: At a Speed of Life!

የአማራ ክልልን የቱሪዝም ዘርፍ ማነቃቃት ዓላማ ያደረገ የድንቅ ምድር እውቅናና የቁንጅና ውድድር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥር 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ክልልን የቱሪዝም ዘርፍ ማነቃቃት ዓላማ ያደረገ “የድንቅ ምድር እውቅናና ሽልማት” እንዲሁም የቁንጅና ውድድር ተካሄደ።

ከፍተኛ የክልሉ የሥራ ኅላፊዎች በተገኙበት በጎንደር  ከተማ አጼ ፋሲል ቤተ መንግሥት ስነስርዓቶቹ ተካሂደዋል፡፡

በዚሁ መሠረትም የመጀመሪያውን የድንቅ መዳረሻ የእውቅና ሽልማት ላሊበላ፣ ጎንደር፣ ባህር ዳር እና ሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ አሸናፊ በመሆን ተመርጠዋል።

ቀጥሎ በተካሄደው “የወይዘሪት ቱሪዝም አማራ” የቁንጅና ውድድር ከሰሜን ሸዋ ዞን ቤዛ ሳህሌ አሸናፊ ሆናለች።

የውድድሩ አሸናፊ “ወይዘሪት ቱሪዝም-አማራ” በመባል የአማራ ክልል የ2015 ዓ.ም የድንቅ ምድር አማራ የባህል አምባሳደር ሆና ተሰይማለች፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.