Fana: At a Speed of Life!

አምባሳደር ሱለይማን ደደፎ የኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ

አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አምባሳደር ሱለይማን ደደፎ የኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ፡፡

አምባሳደር ሱለይማን ከዚህ በፊት በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ባለሙስልጣን አምባሳደር በመሆን ማገልገላቸው ይታወሳል፡፡

በተጨማሪም አቶ መሃመድ ጀማል ሸሪፍ የተቋሙ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኦፕሬሽን ዘርፍ ኃላፊ እና ወ/ሮ መሰረት ደስታ ገ/የሱስ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ የምርምርና ቢዝነስ ዴቬሎፕመንት ዘርፍ ኃላፊ በመሆን ከጥር 7 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ መመደባቸው ተገልጿል ፡፡

የኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕን በዋና ስራ አስፈጻሚነት ሲመሩ የነበሩት አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በቅርቡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው መሾማቸው ይታወሳል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.