Fana: At a Speed of Life!

በኦሮሚያ ክልል በ341 ሰዎች ላይ የሙስና ክስ ተመሰረተ

አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል በ341 ሰዎች ላይ የሙስና ክስ መመስረቱን በክልሉ የተቋቋመው የፀረ-ሙስና ኮሚቴ አስታውቋል።

በክልሉ የተቋቋመው እና ሰባት አባላት ያለው የፀረ-ሙስና ኮሚቴ እያከናወነ ያለውን ተግባር ተኮር ሥራ አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል።

በመግለጫው÷በኦሮሚያ ክልል ከሙስና ጋር በተያያዘ 16 መዝገቦች መከፈታቸውን ኮሚቴው አስታውቋል፡፡

በክልሉ የህብረተሰቡን ጥቆማ ተከትሎ በርካታ ሰዎች በቁጥጥር ስር እየዋሉ ጉዳያቸው እየተጣራ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን÷ በ341 ሰዎች ላይ ክስ እንደተመሰረተባቸው በመግለጫው ተነስቷል፡፡

በተጨማሪም÷ በክልሉ ከሙስና ጋር በተያያዘ የተመዘበሩ የህዝብና መንግስት ንብረቶችን የማስመለስ ስራ እየተሰራ መሆኑንም ኮሚቴው ገልጿል፡፡

የሙስና ወንጀልን ለመከላከል እስካሁን ከኅብረተሰቡ በርካታ ጥቆማዎች እየመጡ መሆናቸው የተነሳ ሲሆን÷ ጥቆማው እውነታን መሰረት ያደረገ እንዲሆን ጥሪ ቀርቧል፡፡

በክልሉ ኮሚቴው ከተቋቋመ ወዲህ 61 የሚሆኑ ጥቆማዎች ከኅብረተሰቡ መምጣታቸው ተመላክቷል።

በበኃይሉ ባኔ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.