የሀገር ውስጥ ዜና

በኢትዮጵያ ተጨማሪ አምስት ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ

By Tibebu Kebede

April 05, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ተጨማሪ አምስት ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን የጤና ሚኒስቴር ገለፀ፡፡

ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ ባለፈው 24 ሰዓታት ውስጥ 59 የላብራቶሪ ምርመራዎች የተደረጉ ሲሆን፥ ከእነዚህም ውስጥ አምስቱ ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል ብሏል።