የጥምቀት በዓል በምጃር ሸንኮራ ወረዳ ኢራቡቲ እየተከበረ ነው
አዲስ አበባ፣ ጥር 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጥምቀት በዓል በምጃር ሸንኮራ ወረዳ በኢራቡቲ በድምቀት እየተከበረ ነው።
በዓሉ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ-ጳጳስ ብፁ ወቅዱስ አቡነ ቀለሚንጦስ በተገኙበት ነው በአምሳለ ዮርዳኖስ እየተከበረ የሚገኘው ።
44ቱ ታቦታት በትላንትናው ዕለት ከየአድባራቱ በካህናቱ፣ በዲያቆናቱ እንዲሁም በምዕመኑ ዝማሬ ታጅበው ወደአምሳለ ዮርዳኖስ ባህረ ጥምቀቱ ከደረሱ ብኋላ የተለያዩ ሃይማኖታዊ ክዋኔዎችን በመፈፀም ታድሯል ፡፡
ዛሬ ጠዋትም የቅዳሴ ስነ-ስርዓቱ ተከናውኖ በብፁ አቡነ ቀለሚንጦስ አምሳለ ዮርዳኖስ ተባርኮ ምዕመኑ ተጠምቋል።
በምጃር ሸንኮራ ኢራቡቲ የጥምቀት በዓል አከባበር ላይም ከአካባቢው ማህበረሰብ በተጨማሪ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ጎብኚዎች ታድመዋል ።
በአበበ የሸዋልዑል