Fana: At a Speed of Life!

በመዲናዋ የትራንስፖርት ታሪፍ ላይ ማሻሻያ ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ጥር 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጥር ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ የተደረገውን የዋጋ ማስተካከያ ግምት ውስጥ በማስገባት የትራንስፖርት ታሪፍ ላይ ማሻሻያ ማድረጉን የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል፡፡

አዲሱ የታሪፍ ማሻሻያ ከነገ ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ ተገልጿል፡፡

በዚህም መሰረት የከተማ አውቶቡሶችን በተመለከተ÷ እስከ 4 ኪሎ ሜትር 1 ብር ከ50 ሣንቲም የነበረው እና ከ4 ነጥብ 1 እስከ 6 ኪሎ ሜትር 2 ብር የነበረው በአዲሱ የታሪፍ ማሻሻያ 3 ብር፣ ከ6 ነጥብ 1 እስከ 8 ኪሎ ሜትር 2 ብር ከ50 ሣንቲም የነበረው እና ከ8 ነጥብ 1 እስከ 9 ኪሎ ሜትር 3 ብር የነበረው ታሪፍ በአዲሱ ማሻሻያ 5 ብር፣ ከ9 ነጥብ 1 እስከ 10 ኪሎ ሜትር 3 ብር ከ50 ሣንቲም የነበረው እና ከ10 ነጥብ 1 እስከ 12 ኪሎ ሜትር 4 ብር የነበረው በአዲሱ የታሪፍ ማሻሻያ 6 ብር እንዲሆን ውሳኔ ተላልፏል፡፡

ከ12 ነጥብ 1 እስከ 13 ኪሎ ሜትር 4 ብር ከ50 ሣንቲም፣ ከ13 ነጥብ 1 እስከ 15 ኪሎ ሜትር 5 ብር የነበረው እንዲሁም ከ15 ነጥብ 1 እስከ 17 ኪሎ ሜትር 6 ብር የነበረው በአዲሱ የታሪፍ ማሻሻያ 8 ብር ሆኗል፡፡

እንዲሁም ከ17 ነጥብ 1 እስከ 20 ኪሎ ሜትር 7 ብር የነበረው 10 ብር እና ከ20 ነጥብ 1 ነጥብ እስከ 23 ኪሎ ሜትር 8 ብር የነበረው 10 ብር እንዲሆን ተወስኗል፡፡

ከ23 ነጥብ 1 እስከ 26 ኪሎ ሜትር 9 ብር የነበረው 15 ብር ፣ ከ26 ነጥብ 1 እስከ 30 ኪሎ ሜት 10 ብር የነበረው 15 ብር፣ ከ 30 ነጥብ 1 እስከ 35 ኪሎ ሜትር 12 ብር የነበረው 20 ብር፣ ከ35 ነጥብ 1 እስከ 40 ኪሎ ሜትር 15 ብር የነበረው 20 ብር፣ ከ40 ነጥብ 1 እስከ 45 ኪሎ ሜትር 15 ብር የነበረው 25 ብር፣ ከ45 ነጥብ 1 እስከ 50 ኪሎ ሜትር 20 ብር የነበረው 25 ብር እንዲሆን ተወስናል፡፡

የሃይገርና የቅጥቅጥ ታክሲዎች የታሪፍ ማሻሻያ በተመለከተ÷ እስከ 8 ኪሎ ሜትር 5 ብር የነበረው ታሪፍ በነበረው እንዲቀጥል፣ ከ8 ነጥብ 1 እስከ 12 ኪሎ ሜትር 7 ብር ከ50 ሣንቲም የነበረው በአዲሱ ማሻሻያ 8 ብር፣ ከ12 ነጥብ 1 እስከ 16 ኪሎ ሜትር 9ብር ከ50 ሣንቲም የነበረው ታሪፍ ከነገ ጀምሮ በሚተገበረው ማሻሻያ 10 ብር እንዲሆን ተደርጓል፡፡

በተጨማሪም ከ16 ነጥብ 1 እስከ 20 ኪሎ ሜትር 12 ብር የነበረው ክፍያ በአዲሱ የታሪፍ ማሻሻያ 13 ብር እንዲሁም ከ20 ነጥብ 1 እስከ 24 ኪሎ ሜትር 14 ብር ከ50 ሣንቲም የነበረው በአዲሱ የታሪፍ ማሻሻያ 15 ብር፣ ከ24 ነጥብ 1 እስከ 28 ኪሎ ሜትር 17 ብር የነበረው 18 ብር እንዲሆን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ውሳኔ አሳልፏል፡፡

ከ7 ነጥብ 6 እስከ 10 ኪሎ ሜትር 13 ብር የነበረው ታሪፍ በማሻሻው 14 ብር፣ ከ10 ነጥብ 1 እስከ 12 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር 16 ብር ከ50 ሣንቲም የነበረው ታሪፍ 17 ብር፣ ከ12 ነጥብ 6 እስከ 15 ኪሎ ሜትር 19 ብር ከ50 ሣንቲም የነበረው ታሪፍ 20 ብር ከ50 ሣንቲም እንዲሆን ተወስኗል፡፡

ከ15 ነጥብ 1 እስከ 17 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር 23 ብር የነበረው 24 ብር፣ ከ17 ነጥብ 6 እስከ 20 ኪሎ ሜትር 26 ብር ከ50 ሣንቲም የነበረው በአዲሱ ማሻሻያ 27 ብር፣ ከ20 ነጥብ 1 እስከ 22 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር 29 ብር ከ50 ሣንቲም የነበረው ታሪፍ በማሻሻያው 31 ብር ሆኗል፡፡

እንዲሁም ከ22 ነጥብ 6 እስከ 25ኪሎ ሜትር 33 ብር የነበረው ታሪፍ በማሻሻያው 34 ብር፣ ከ25 ነጥብ 1 እስከ 27 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር 36 ብር የነበረው ታሪፍ 38 ብር፣ ከ27 ነጥብ 6 እስከ 30 ኪሎ ሜትር 39 ብር ከ50 ሣንቲም የነበረው ታሪፍ በአዲሱ ማሻሻያ 41 ብር መሆኑ ተገልጿል፡፡

የሚኒባስ ታክሲዎችን በተመለከተ÷ እስከ 2 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር 3 ብር ከ50 ሣንቲም የነበረው በተስተካከለው ታሪፍ 4 ብር፣ ከ2 ነጥብ 6 እስከ 5ኪሎ ሜትር 6 ብር ከ50 ሣንቲም የነበረው ታሪፍ በአዲሱ የታሪፍ ማሻሻያ 7 ብር ሆኗል፡፡

በተጨማሪም ከ5 ነጥብ 1 እስከ 7 ነጥብ 5ኪሎ ሜትር 10 ብር የነበረው ታሪፍ በተመሳሳይ 10 ብር ሆኖ እንዲቀጥል ተወስኗል፡፡

የአዲስ አበባ ቀላል ባቡርን በተመለከተ÷ እስከ 17 ኪሎ ሜትር 4 ብር የነበረው በአዲሱ የታሪፍ ማሻሻያ 7 ብር እንዲሆን ቢሮው ውሳኔ አሳልፏል፡፡

በምስክር ተስፋዬ
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.