Fana: At a Speed of Life!

ለአትሌት ታምራት ቶላ የምክትል ኮማንደርነት ማዕረግ ተሰጠ

 

አዲስ አበባ፣ ጥር 14፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ለአትሌት ታምራት ቶላ የምክትል ኮማንደርነት ማዕረግ ሰጠ፡፡

ኮሚሽኑ በዛሬው ዕለት ለ46 አትሌቶቹ የተለያዩ ማዕረጎችን ሰጥቷል፡፡

በዚህም በኦሪገን ማራቶን ሻምፒዮን የነበረው አትሌት ታምራት ቶላ የዋና ሳጅን ማዕረግ የነበረው ሲሆን÷ በዛሬው ዕለት የምክትል ኮማንደርነት ማዕረግ ተሰጥቶታል፡፡

በመርሃ ግብሩ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ምክትል ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉን ጨምሮ የተለያዩ አመራሮች ተገኝተዋል፡፡

ኮሚሽኑ ታላላቅ አትሌቶችን እያፈራ ያለ መሆኑም በመድረኩ ተገልጿል፡፡

በሂርፖ ሺቦ

 

 

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.