Fana: At a Speed of Life!

አቶ አሻድሊ ሀሰን ለመልሶ-ማቋቋም የሚተገበር ፕሮጀክትን በይፋ አስጀመሩ

አዲስ አበባ ፣ ጥር 17 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በጸጥታ ችግር የተጎዱ መሠረተ ልማቶችን መልሶ ለማማቋቋም የሚያስችል ፕሮጀክት በርዕሰ-መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ይፋ ተደርጓል።

የመጀመሪያ ምዕራፍ የመልሶ ማቋቋም ፕሮጀክቱ የክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰንን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በመተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ ፎቶማንጀሪ ቀበሌ ነው ይፋ የተደረገው።

አቶ አሻድሊ ሃሰን ፕሮጀክቱን በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት÷ የክልሉ መንግስት ወደቀያቸው የተመለሱ ዜጎችን በዘላቂነት ለማቋቋም እና የተጎዱ መሠረተ-ልማቶችን መልሶ ለማቋቋም በጥናት ላይ የመሠረተ ሥራ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።

ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ ሁሉም የበኩሉን ሊወጣ ይገባል ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ÷ በቀጣይ በሌሎች አካባቢዎች መሠል ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።

የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ምክትል ሃላፊ ወይዘሮ ትዕግስት ዲቢሳ በበኩላቸው÷ የወደሙ ተቋማትንና ዜጎችን በዘላቂነት ለማቋቋም 155 ሚሊየን ብር መነሻ በጀት መያዙን ጠቁመዋል።

በመጀመሪያው ዙር የፕሮጀክቱ ትግበራ ማንዱራ፣ ቡለንና ሰዳል ወረዳዎች ተደራሽ የሚደረጉ ሲሆን÷ መሰረታዊ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማትን ለማደስና በአዲስ መልክ ለመገንባት እንደሚሠራም ነው የገለጹት።

በተጨማሪም ፕሮጀክቱ ህብረተሰቡን በስነ-ልቦና የማጠናከር እና በኑሮ በዘላቂነት የማቋቋም ዓላም እንዳለው መጥቀሣቸውን ከመተከል ዞን ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

አምስት ዓመት ቆይታ ያለው ፕሮጀክቱ ከዓለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚተገበርም ተገልጿል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.