Fana: At a Speed of Life!

ጠ/ሚ ዐቢይ ከሱዳን የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ከሦስትዮሽ መፍትሔ አፈላላጊ ቡድን አባላት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥር 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሱዳን ቆይታቸው በፖለቲካው ሂደት ላይ ከተሰማሩ የተለያዩ የሱዳን የፖለቲካ ፓርቲዎች እና ከሦስትዮሽ መፍትሔ አፈላላጊ ቡድን አባላት ጋር ተወያዩ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በውይይታቸው የኢትዮጵያ ጣልቃ ገብ ያልሆነ መርሕ ለራሷ ብቻ ሳይሆን ለሌሎችም ጭምር የሚሠራ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡

የሱዳን ሕዝብ እና ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች ሀገር በቀል መፍትሔዎችን እንዲፈልጉም ማበረታታቸውንም የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለሥራ ጉብኝት ወደ ሱዳን ካርቱም ማቅናታቸው ይታወቃል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.