Fana: At a Speed of Life!

2 ሚሊየን ኩንታል ስኳር ከውጭ በቅርቡ ይገባል

አዲስ አበባ፣ ጥር 19፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2 ሚሊየን ኩንታር ስኳር በቅርቡ ከውጭ እንደሚገባ የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ አስታወቀ፡፡

ለግዥውም 110 ነጥብ 4 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር ወጪ መደረጉ ተገልጿል፡፡

ስኳሩም ከብራዚል መገዛቱን ነው በኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የሕዝብ ግንኙነትና ተሳትፎ ዋና ክፍል ኃላፊ ረታ ደመቀ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የገለፁት።

የስኳር ምርቱ በአራት ዙር ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገባም ነው የጠቆሙት፡፡

ከግዥ ጋር በተያያዘ በተቋሙ በኩል ያሉ ስራዎች ሙሉ በሙሉ መጠናቀቃቸውን አረጋግጠዋል፡፡

በዮሐንስ ደርበው

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.