Fana: At a Speed of Life!

1 ሺህ 176 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ጥር 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ በሶስት ዙር በተከናወነ በሳዑዲ አረቢያ በችግር ውስጥ ያሉ ዜጎችን የመመለስ ስራ 1 ሺህ 176 ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው መመለስ መቻሉ ተገለፀ፡፡

በዛሬው እለት ከተመለሱት ዜጎች መካከል 1 ሺህ 167ቱ ወንዶች፣ ዘጠኙ እድሜያቸው ከ18 አመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች መሆናቸው ታውቋል።

ለተመላሽ ዜጎች በአውሮፕላን ማረፊያና በማቆያ ማእከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ከቤተሰብ ጋር የመቀላቀል ስራ እየተሰራ እንደሚገኝ ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ከህዳር 12 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ እስካሁን በተከናወነ ዜጎችን ወደ ሀገር የመመለስ ስራ 36 ሺህ 425 ኢትዮጵያውያንን መመለስ ተችሏል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.