የሀገር ውስጥ ዜና

የአዲስ አበባ ውኃና ፍሳሽ ባለስልጣን በ15 ሚሊየን ዶላር የተገዙ የፍሳሽ ማንሻ ተሽከርካሪዎችን ተረከበ

By ዮሐንስ ደርበው

February 06, 2023

አዲስ አበባ፣ ጥር 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለስልጣኑ የፍሳሽ ቆሻሻ የማንሳት አገልግሎቱን የላቀ ለማድረግ ከዓለም ባንክ በተገኘ 15 ሚሊየን ዶላር ብድር የገዛቸውን 90 የፍሳሽ ማንሻ ተሽከርካሪዎች ተረከቧል፡፡

የባለስልጣኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ሰርካለም ጌታቸው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ ተሽከርካሪዎቹ ዘመናዊ የፍሳሽ በመስመር ማስወገድ አገልግሎት ተደራሽ ባልሆነባቸው አካባቢዎች ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ያደርጋሉ፡፡

የባለስልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ዘሪሁን አባተ ተሸከርካሪዎቹን ወደ ሥራ ለማስገባት በተካሄደ ስልጠና ላይ እንደተናገሩት÷ ተሽከርካሪዎቹ የሚነሳውን የፍሳሽ መጠን ከማሳደግ ጎን ለጎን በወረፋ ምክንያት ያልተስተናገዱ ደንበኞችን ችግር ይቀርፋሉ፡፡

ባለሙያዎችም ተሽከርካሪዎቹ ያለ ችግር ረጅም ጊዜ እንዲያገለግሉ የድርሻቸውን እንዲወጡም አስገንዝበዋል።

በዮሐንስ ደርበው

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/ ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!