የሀገር ውስጥ ዜና

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በኮሮናቫይረስ ዙሪያ የሚሰሩ የፈጠራ ስራዎችን በገንዘብ ለመደገፍ ከዩ.ኤን.ዲ.ፒ ጋር ተስማማ

By Tibebu Kebede

April 07, 2020

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በኮሮና ቫይረስ ዙርያ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም (ዩ.ኤን.ዲ.ፒ) ጋር ለመስራት የሚያስችል ስምምነት መረፋፈሙን አስታወቀ።

ስምምነቱ በኮሮና ቫይረስ ዙሪያ የሚሰሩ ኢኖቬሽን ተኮር የምርምርና ፈጠራ ስራዎችን በገንዘብ ለመደገፍ የሚያስችል መሆኑንም ሚኒስቴሩ ባወጣው መረጃ አስታውቋል።