Fana: At a Speed of Life!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ማክሮን ጋር በፓሪስ መከሩ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከፈረንሳይ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር በፓሪስ መከሩ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአውሮፓ ጉብኝታቸው ከጣሊያን እና ማልታ በመቀጠል ፈረንሳይ፣ ፓሪስ ገብተዋል።

በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባወጡት መግለጫም “ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮንን በማግኘቴ ደስ ብሎኛል” ብለዋል።

“በፓሪስ ስለተደረገልን አቀባበል እናመሰግናለን” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፥ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት እየጠነከረ ሲሄድ፥ ወደ ላቀ ኢኮኖሚያዊ ውጤት እንደሚሸጋገር እምነታቸው መሆኑን ገልፀዋል።

የፈረንሳይ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ የሚያደርጉትን ኢንቨስትመንት እንደሚያበረታቱም አስታውቀዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.