Fana: At a Speed of Life!

በመተከል ዞን የእርቀ ሰላም ስምምነት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በመተከል ዞን ዳንጉር ወረዳ በአራት ቀበሌዎች ሲንቀሳቀሱ ከነበሩ ፀረ ሰላም ኃይሎች ጋር የእርቀ ሰላም ስምምነት ተካሄደ፡፡

በመከላከያ ሰራዊት የሜካናይዝድ ክፍሉ ስነልቦና ግንባታ ኃላፊ ሻለቃ መስፍን አስራት÷ መንግስት የሰጠው የሰላም አማራጭ ውጤታማ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የተደረገው የሰላም ስምምነት ለሀገር እድገትና አንድነት ትልቅ ዋጋ አለው ማለታቸውን ከመከላከያ ሰራዊት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

የዳንጉር ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ፓርሻዊ ኡስማን እንደገለጹት÷ በፀጥታ ኃይሉ የተገኘውን ዘላቂ ሰላም በማስጠበቅ ለዘላቂ ልማት የሚደራጅ አምራች ኃይል እየፈጠሩ መቀጠል ይገባል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.