Fana: At a Speed of Life!

42ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብስባ ተጀመረ

አዲስ አበባ የካቲት 8 2015 (ኤፍ ) 42ኛው የአፍሪካ ሕብረት የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤት ስብሰባ ዛሬ አዲስ አበባ ተጀምሯል።

በምክር ቤቱ ስብስባ ላይ የሕብረቱ አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና ተወካዮች ይሳተፋሉ።

 በስብስባው ላይ ለመሳተፍ ከተገኙት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች መካከል የሶማሊያ፣ ናይጄሪያ፣ ኮሞሮስ፣ ታንዛንያ፣ ኢስዋቲኒ፣ ሴራሊዮን፣ ኮትዲቭዋር፣ ማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ዚምባቡዌ እና ማሊ ይገኙበታል።

የምክር ቤቱ ስብሰባ የአፍሪካ ሕብረት ቋሚ ተወካዮች ኮሚቴ በጥር ወር 2015 . በአዲስ አበባ ባደረገው 45 መደበኛ ስብስባ የተወያየባቸው አጀንዳዎች እንደሚቀርቡበት ሕብረቱ አስታውቋል።

ምክር ቤቱ ለሁለት ቀናት በሚያደርገው ስብሰባ በኮሚቴው የቀረቡለትን የተለያዩ አጀንዳዎች ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

ምክር ቤቱየአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና ትግበራን ማፋጠንየአፍሪካ ሕብረት .. 2023 መሪ ሃሳብ ሆኖ እንዲሰየም በቀረበው የመነሻ ሃሳብ ላይ እንደሚወያይ የአፍሪካ ሕብረት አስታውቋል።

የስራ አስፈጻሚ ምክር ቤቱ በውይይቱ ያጸደቃቸውን አጀንዳዎች 36ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ያቀርባል።

የሕብረቱ የመሪዎች ጉባኤ የካቲት 11 እና 12 ቀን 2015 . እንደሚካሄድ ኢዜአ ዘግቧል።

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.