Flags of India and ethiopia inside chat bubbles isolated on white. 3D illustration

የሀገር ውስጥ ዜና

በህንድ የሚማሩ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል ከ250 ሺህ ብር በላይ ለገሱ

By Tibebu Kebede

April 09, 2020

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 1፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በህንድ የሚማሩ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል ከ250 ሺህ ብር በላይ ለገሱ።

በሀገሪቱ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ ከ1 ሺህ የሚበልጡ ተማሪዎች ናቸው በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የሚውል የገንዘብ ድጋፍ ያደረጉት።

በህንድ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ዶክተር ትዝታ ሙሉጌታ እንደገለጹት፥ ኤምባሲው በኢሜል፣ በፌስቡክ፣ በተማሪ አደረጃጀት እንዲሁም በምስል የተቀነባበረ ዘዴ በመጠቀም ለተማሪዎቹ ስለወረርሽኙ አስከፊነትና ጥንቃቄ እያስገነዘበ ነው።

የቫይረሱ ስርጭት በቁጥጥር ስር እስከሚውል ድረስም ይህ ስራ እንደሚቀጥል አምባሳደር ትዝታ ተናግረዋል።

ተማሪዎቹ ላደረጉት የገንዘብ ድጋፍ በኤምባሲው ስም አምባሳደሯ ምስጋና አቅርበዋል።