Fana: At a Speed of Life!

በፌደራል ፍርድ ቤቶች ከሚታዩ አስቸኳይ ጉዳዮች ውስጥ የቤት ውስጥ ጥቃት ክስ አንዱ እንዲሆን መመሪያ ተሰጠ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 1፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በፌደራል ፍርድ ቤቶች ከሚታዩ ጥቂት አስቸኳይ ጉዳዮች ውስጥ የቤት ውስጥ ጥቃት ክስ አንዱ እንዲሆን መመሪያ መሰጠቱን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ወይዘሮ መዓዛ አሸናፊ ገለፁ።

ወይዘሮ መዓዛ አሸናፊ በትዊተር ገፃቸው እንዳስታወቁት፥ የኮሮና ስርጭትን ለመከላከል ህብረተሰቡ በቤት በሚቆይበት ወቅት በቤት ውስጥ የሚፈፀሙ ጥቃቶች ሊጨምሩ እንደሚችሉ በማሰብ መመሪያው የወጣው።

በመመሪያው መሰረትም የፌደራል ፍርድ ቤቶች የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ስርጭትን ለመከላከል በከፊል ዝግ ሆነው በሚቆዩባቸው ጊዜያት ከሚያዩቸው ጥቂት አስቸኳይ ጉዳዮች ውስጥ የቤት ውስጥ ጥቃት ክስ እንዲሆን መመሪያ መሰጠቱን ነው የገለፁት።

ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
https://t.me/fanatelevision

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.