Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ ወደ ቱርክ የላከችው የቁሳቁስ ድጋፍ እና የነፍስ አድን ቡድን ጋዛንቴፕ ደረሰ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በቱርክ በተከሰተው ርዕደ መሬት ምክንያት ትናንት ወደ ቱርክ የላከችው የቁሳቁስ እና የነፍስ አድን ቡድን አደጋው በደረሰበት ጋዛንቴፕ መድረሱ ተገለጸ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቱርክ በተከሰተው የርዕደ መሬት አደጋ የተሰማቸው ጥልቅ ሃዘን ገልጸው÷ ኢትዮጵያ የተቸገረ ወዳጅዋን ለመርዳት ምንጊዜም ቁርጠኛ መሆኗን አስታውቀው ነበር፡፡

በዚሁ መሰረት ትናንት አመሻሽ ላይ ኢትዮጵያ ወደ ቱርክ የላከችው የቁሳቁስ ድጋፍ እና የነፍስ አድን ቡድን አደጋው በደረሰበት ጋዛንቴፕ መድረሱን በቱርክ የኢትዮጵያ አምባሳደር አደም ሞሐመድ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.