ከ60 ዓመት የዕድሜ ባለጸጋ እናት 8 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕጢ ተወገደ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጦራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ከ60 ዓመት የዕድሜ በለጸጋ እናት 8 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕጢ ማስወገድ መቻሉ ተገልጿል፡፡
በሆስፒታሉ ስኬታማ ነው የተባለለትን ቀዶ ጥገና ያደረጉት እና የቀዶ ጥገናውን ቡድን የመሩት የማህጸን እና ጽንስ ስፔሻሊስት ዶክተር ጌታቸው የተባሉ ሐኪም መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡
ቀዶ ጥገናው 2 ሠዓት ከ 20 ደቂቃ እንደፈጀም ከሆስፒታሉ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ቀዶ ጥገና የተደረገላቸው እናት ከቀዶ ጥገናው በኋላ በመልካም ጤንነት ላይ ይገኛሉ ተብሏል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!