Fana: At a Speed of Life!

በመዲናዋ ዓለም አቀፍ የእምነት ተቋማት ትብብር ጉባዔ ሊካሄድ ነው

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ የካቲት 21 ቀን 2015 ዓ.ም ዓለም አቀፍ የእምነት ተቋማት ትብብር ጉባዔ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ አስታወቀ፡፡

የጉባዔው ዓላማ ÷ በቤተ እምነቶች መካከል ያለውን ትብብር ማጠናከር፣ በአማኞች መካከል መግባባትን ማጎልበት ነው፡፡

የሃይማኖት ተቋት ጉባዔ ዛሬ በሰጠው መግለጫ እንዳስታወቀው÷ የዓለም አሁናዊ ፈተናዎች ላይ ምክክር ያደርጋል የተባለው ጉባዔው ለፖሊሲ አውጪዎች የመፍትሄ ሀሳቦችን ያቀርባል።

ጉባዔው በየዓመቱ ከአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ ማግስት እንደሚካሔድም ተገልጿል።

በወንድሙ አዱኛ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.