Workers arrange a garden at the Friendship Square in the city of Addis Ababa, Ethiopia, on September 22, 2020. - For the past year, workers have been busy transforming a disused plot of land down the hill from Ethiopian Prime Minister Abiy Ahmed's office into a park showcasing his political vision. The 48-hectare Friendship Square is rich in symbolism promoting unity. (Photo by EDUARDO SOTERAS / AFP) (Photo by EDUARDO SOTERAS/AFP via Getty Images)

የሀገር ውስጥ ዜና

ባለሃብቶች በመዲናዋ በተለያዩ ዘርፎች መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ በትኩረት እየተሰራ ነው

By Melaku Gedif

February 23, 2023

አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለሃብቶች በአዲስ አበባ ከተማ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የአዲስ አበባ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

በኮሚሽኑ የእቅድና በጀት ዳይሬክተር እናትነሽ ታመነ እንደገለጹት ÷ በመዲናዋ በተለያዩ ዘርፎች መዋዕለ ንዋያቸውን ለሚያፈሱ የውጭና የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች አስፈላጊው ድጋፍና ክትትል እየተደረገ ነው፡፡

በግማሽ ዓመቱ 3 ሺህ 150 ባለሃብቶች አዲስ የኢንቨስትመንት ፈቃድ እንዲወስዱ፣ እንዲያድሱ እና እንዲያሻሽሉ ለማድረግ ታቅዶ 2 ሺህ 863 ማከናወን መቻሉን አንስተዋል፡፡

በዚህም የእቅዱን 90 በመቶ ኢንቨስትመንት መሳብ መቻሉን ጠቁመው÷ለ2 ሺህ 834 ዜጎችም ቋሚ እና ጊዜያዊ የስራ እድል መፈጠሩን ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም ለ424 ፕሮጀክቶች እና ወጪ ምርቶችን የሚያሳድጉና ገቢ ምርቶችን ለሚተኩ 15 ተቋማት ክትትል እና ድጋፍ መደረጉን ወ/ሮ እናትነሽ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል፡፡

የኮሚሽኑ የደንበኞች አገልግሎት አሰጣጥ በቴክኖሎጂ የተደገፈ መሆኑን የገለጹት ዳይሬክተሯ ÷ በዚህም ፈጣን እና ቀልጣፋ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን አንስተዋል፡፡

ለአልሚዎች አስፈላጊ ግብዓቶችን እና መሰረተ ልማቶችን ከማሟላት አንጻርም ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በትስስር እንደሚሰራ አስረድተዋል፡፡

የውጭ እና የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች በመዲናዋ አሁን ላይ ያለውን አስተማማኝ ጸጥታና የመሰረት ልማት ዝርጋታ ግምት ውስጥ በማስገባት መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱም ጥሪ አቅርበዋል፡፡