Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያ 2ኛውን በሠራተኞች ላይ የሚመክር የሚኒስትሮች ጉባዔ እንደምታስተናግድ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ በሠራተኞች ፣ በሥራ እና ፍልሰት ላይ የሚመክረውን 2ኛውን የሚኒስትሮች ጉባዔ ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ እንደምታስተናግድ ተገለጸ፡፡

በኢጋድ አባል ሀገራት ውስጥ ሥራ እና የሠራተኞች ጉዳዮች ላይ የሚሠሩ ሚኒስትሮች በአንድ ላይ እንደሚሰባሰቡ እና ጅቡቲ የተፈረመው ስምምነት አፈጻጸም ላይ እንደሚመክሩ የዓለምአቀፍ የሠራተኞች ድርጅት መረጃ ጠቁሟል፡፡

የጅቡቲው ሥምምነት የሚያተኩረው ስደተኞች እና ልጆቻቸውን ማስተማር ላይ መሆኑም ተመልክቷል፡፡

ጉባዔው በፈረንጆቹ መጋቢት 2 ቀን ይጠናቀቃል ተብሏል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.